ለሕብረት ኢንሹራንስ አ.ማ ባለአክስዮኖች በሙሉ

ለሕብረት ኢንሹራንስ አ.ማ ባለአክስዮኖች በሙሉ

ዕጩ የዲሬክተሮች ቦርድ አባላት ጥቆማ ለመቀበል የወጣ ማስታወቂያ

የሕብረት ኢንሹራንስ አ.ማ ባለአክስዮኖች ባካሄዱት 26ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ  የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ ቁጥር SIB/48/2019 መሠረት የቦርድ አባላት አስመራጭ ኮሚቴ መመረጡ ይታወቃል፡፡

በዚሁ መሠረት ኮሚቴው ዕጩ የዲሬክተሮች ቦርድ አባላትን ጥቆማ ከሰኔ 21 ቀን 2013 ዓ.ም  እስከ መስከረም 18 ቀን 2014 ዓ. العاب مقابل المال ም ብቻ ስለሚቀበል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያዎች በተለይም ቁጥር       SIB/48/2019 እና  SIB/32/2012 ላይ የተዘረዘሩትንና በሚከተለው ሁኔታ የቀረቡትን መስፈርቶች የሚያሟሉ እጩዎችን እንድትጠቁሙ ለመላው የኩባንያችን ባለአክስዮኖች ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

  1. የሕብረት ኢንሹራንስ ባለአክስዮን የሆነና የቦርድ አባል ሆኖ ለመስራት ፈቀደኛ የሆነ፣
  2. ዕድሜው 30 አመትና ከዚያ በላይ የሆነ፣
  3. በንግድ ሥራ አመራር የሥራ ልምድ ያለው፣ በተለይም በኢንሹራንስ ሥራ ልምድ ያለው ቢሆን ተመራጭ ይሆናል፡፡
  4. በማንኛውም ኢንሹራንስ ኩባንያ ሠራተኛ ያልሆነ፣
  5. ሀቀኛ፣ ታማኝና መልካም ዝና ያለው፣ በተለይም በማጭበርበር፣ እምነት በማጉደል፣ ትክክለኛ ያልሆነ የሂሳብ መግለጫ በማቅረብና በመሳሰሉት ተከሶ በፍርድ ቤት የጥፋተኝነት ውሳኔ ተሰጥቶበት የማያውቅ፣
  6. በሌላ የፋይናንስ ድርጅት ውስጥ የቦርድ አባል ያልሆነ፣
  7. በራሱ ወይም በሚመራው ወይም ዳይሬክተር በሆነበት ድርጅት ላይ የመክሰር ክስ ያልቀረበበት ወይም የኪሳራ ውሳኔ ያልተሰጠበት፣
  8. በኪሳራ ምክንያት ንብረቱ የእዳ ማቻቻያ ሆኖ ያልተወሰደበት፣
  9. የባንክ ብድር ባለመክፈሉ ምክንያት ንብረቱ በሐራጅ ያልተሸጠ፣ ተከሶ ያልተፈረደበት ወይም እሱ የሚመራው ወይም ዳይሬክተር የሆነበት ድርጅት ከገንዘብ ተቋማት የተበደረውን ገንዘብ ባለመክፈሉ ብድሩ ጤናማ ወዳልሆነ የብድር ሁኔታ ያልገባበት (NPL ያልሆነበት)፣
  10. ከሚመረጡት የቦርድ አባላት 75% የመጀመሪያ ዲግሪ ወይም ከዚያ በላይ ሊኖራቸው የሚገባ ሲሆን የተቀሩት 25% ቢያንስ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ያጠናቀቁ መሆን አለባቸው፡፡
  11. በቂ ስንቅ/ገንዘብ ሳይኖረው ቼክ ሰጥቶ ሂሳቡ ያልተዘጋበት፣
  12. ታክስ ባለመክፈል ተከሶ ጥፋተኛ ያልተባለ፣
  13. የቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ አባል ያልሆነ እና፣
  14. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያዎች ላይ የተገለጹ ሌሎች መመዘኛዎችን የሚያሟላ፡፡

በመሆኑም ጥቆማውን “ዕጩ የቦርድ አባላትን ለመጠቆም የተዘጋጀ ቅጽ” በሚል የተዘጋጀውን ፎርም በመሙላት

*ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው የሕብረት ኢንሹራንስ አ.ማ. (ኩባንያ) ዋና መስሪያ ቤት 10ኛ ፎቅ የዋና ሥራ አስኪያጅ ፀሐፊ ቢሮ በተዘጋጀው መዝገብ ላይ በአካል ቀርቦ በማስመዝገብ መስጠት ፣ ወይም

* በመልዕክት ሳጥን ቁጥር 1156 ለሕብረት ኢንሹራንስ አ.ማ የዲሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ ጽ/ቤት በማለት መላክ ፣ ወይም

* በኢ-ሜይል አድራሻችን nominationc@unic-ethiopia.com መላክ ይቻላል፡፡

ማሳሰቢያ

  1. የጥቆማ ማቅረቢያውን ቅጽ
  • ከሕብረት ኢንሹራንስ አ.ማ. ዋና ሥራ አስኪያጅ ፀሐፊ ቢሮ ወይም በኩባንያው ቅርንጫፍ መ/ቤቶች ወይም ከኩባንያው ድረ ገጽ www.unic-ethiopia.com ማግኘት ይቻላል፡፡

በተጨማሪም ቅጹ ባለአክስዮኖች በአክስዮን ግዢ ጊዜ ባስመዘገቡት የፖስታ አድራሻ ይላካል፡፡

  • ከመስከረም 18 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት በኋላ የሚቀርቡም ሆነ ከዚህ በኃላ በፖስታ ወይም በኢ-ሜይል የሚደርሱ ጥቆማዎች ተቀባይነት አይኖራቸውም፡፡
  • የሕግ ሰውነት ያለው ባለአክስዮን ጥቆማ ሲያደርግ በጥቆማ ማቅረቢያ ቅጹ ላይ የተገለፁትን ማሳሰቢያዎች ተግባራዊ ማድረግ ይኖርበታል፡፡
  • በተባዕት ጾታ የተገለፀው በሙሉ ለአነስታይ ጾታም ያገለግላል፡፡
  • ከሚጠቆሙት ዕጩዎች መካከል 1/3ኛ የሚጠቆሙት ከኩባንያው ጠቅላላ የተፈረመ አክስዮን ውስጥ ከ2% በላይ በያዙ ባለአክስዮኖች ነው፡፡ የተቀሩት 2/3ኛ ዕጩዎች ደግሞ በሁሉም ባለአክስዮኖች የሚጠቆሙ ናቸው፡፡
  • ለተጨማሪ ማብራሪያና አስተያየት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፀሐፊ ቢሮ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 0114671874 መደወል ይቻላል፡፡

የዲሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ

ሕብረት ኢንሹራንስ አ.ማ.